የሕይወት ትምህርቶች

የስኬታማ ሴቶች ታሪክ

Image

እሌኒ ገብር መድህን

ዶ/ር እሌኒ ገብረመድህን የተወለዱት አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ። የልጅነት እና ወጣትነት ጊዜያቸውንም ከኢትዮጲያ በተጨማሪ ኬንያ ፣ ታንዛኒያ እና ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ በአራት የተለያዩ የአፍሪካ ሀገሮች እየተዘዋወሩ አሳልፈዋል፡፡ ስዋሂሊ ፣ እንግሊዝኛ ፣ አማርኛ እና ፈረንሳይኛ አቀላጥፋ ይናገራሉ ፡፡ ኬንያ ውስጥ ከሚገኘው ሪፍት ቫሊ አካዳሚ ከፍተኛ ክብር ባለው ማእረግ ተመርቀዋል ፡፡ በስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ በተግባራዊ ኢኮኖሚክስ ፒኤችዲ ፣ በሚሺገን ስቴት ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን እና በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ትምህርታቸውን ደግሞ ከኮርኔል ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል። ዶ/ር እሌኒ ገብረመድህን በ የኢትዮጵያ ምርት ገበያን በማቋቋም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለሀገራቸው አበርክተዋል።

Image

መአዛ አሸናፊ

ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ የተወለዱት በ አሶሳ፣ኢትዮጵያ ሲሆን የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን እዛው በ አሶሳ ያጠናቀቁ ሲሆን ከ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ በ ህግ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በ international relations and gender studies አግኝተዋል። ወ/ሮ መአዛ የ ኢትዮጵያ ሴቶች ህግ ባለሙያዎች ማህበርን ያቋቋሙ ሲሆን ይህም ማህበር ለሴቶች መብት መከበር እጅግ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በ ኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት የ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሆነው እያገለገሉ ይገኛሉ።